|
|
ሐረሪዎች ማኅበራዊና ሃይማኖታዊ እንዲሁም ባህላዊ ተግባራቸውን ጠብቀው ለረጅም ጊዜ ያቆያቸውና ለወደፊትም ዋስትና ከሚሰጣቸው ተግባራቸው መካከል አንዱ "ዚያራ" ማድረጋቸው ነው፡፡ |
ሐረሪዎች ማኅበራዊና ሃይማኖታዊ እንዲሁም ባህላዊ ተግባራቸውን ጠብቀው ለረጅም ጊዜ ያቆያቸውና ለወደፊትም ዋስትና ከሚሰጣቸው ተግባራቸው መካከል አንዱ "ዚያራ" ማድረጋቸው ነው፡፡ "ዚያራ" ማለት "አዋች" ወይም "ኢናያች" ጉብኝት ነው፡፡ ከዚህ ቀደም የአዋች እና ኢናያች ትርጉም የተጠበቀ ሆኖ ለምድራዊውም ሆነ ለመንፈሳዊ ሕይወት ተገቢነት ያለውን ሰብዕናቸው በአርአያነት ለመጎናፀፍ የሚደረግ ተግባር ነው፡፡
አዋች ሆኑ ኢናያች የተለያዩ ጎብኚዎችን ስለሚያስተናግዱ በቦታው ለጎብኚዎች አስተማሪ፣ መካሪ፣ መንፈሳዊ ሕይወትን አዳሽና ቀስቃሽ እና አስታዋሽ ይሆናሉ፡፡ እነሱም በአገሬው አጠራር ሙሪድ ይባላሉ፡፡
ሙሪድ ባለበት ወይም የሚገኝበት አዋችም ሆኑ ኢናያች ኃላፊነት የሚሰማው ጎብኚዎችን ማስተማር /ማስረዳት/ የሚችል ቦታውን ከጉዳት የሚጠብቅ ሆኖ ባብዛኛው ከቅድመ አያቶች ሲወርድ የተያያዘ የሥጋ ዝምድና ያላቸው ናቸው፡፡
የዚያራ ትግበራ ለጉብኘት ወደ አዋች የሚሄዱ ግለሰብ እንደአቅሙ /ችሎታው/ ስጦታ ያበረክታሉ፡፡ ይህም ገቢ ለአስተዳዳሪዎች እንዲሁም ለምስኪኖች በሙሪዱ አማካይነት ይከፈላል፡፡ ስጦታን የማበርከት ግዴታ በማንም ጎብኚ የለበትም፡፡ መጠኑም በሰጪው ፍላጎት መሠረት ነው፡፡
ሐረሪዎች ንፁህ ናቸው፡፡ ቤታቸውንና አካባቢያቸውን በየዕለቱ የማፅዳት ባሕል አላቸው፡፡ ንፁህ አካባቢ ማራኪ መአዛ ማጠን ልምዳቸው፤ በአዋችም ሆነ በኢናያች ይስተዋላል፡፡ በንፁህና ማራኪ መአዛ በታወደው ቦታ መንፈሳዊ ጥንካሬን በማበረታታት ወደ ፈጣሪያቸው አቤት ይላሉ፡፡ ለዚህም ነው እጣን ከቤታቸው የማያጡት፡፡ በየአዋቹም በዚሁ የሚታወደው ለሙስሊሙ ዱአ ማድረግ ከሃይማኖታዊ ተግባራት መካከል አንዱ ነው፡፡ ዱአ ማለት ከፈጣሪ በጎን ለማግኘት የሚደረግ ፀሎት ማለት ነው፡፡ ዱአ ለማድረግ ደግሞ መልካም ጠረንና ደስታን የሚያውድ፣ መንፈስን ወደ ፈጣሪ ልብን የሚያረጋጋ ሽታ አስፈላጊ በመሆኑ ዕጣን /ሊባነት/ ዑድ ለዚህ ያገለግላሉ፡፡ (መፍቱህ ዘከሪያ እብዱላሂ ኑር፤ የከተማ ባሕል መፍለቂያ፣ 2000
|